View in English alphabet 
 | Monday, September 06, 2010 ..:: ኪነ ጥበብ ::.. Register  Login
if ye have word of exhortation for the people, say on

በገሊላ ቃና በዶኪማስ ቤት
ድንግል አዛኝቱ የአምላክ እናት
እድምተኛው  በዝቶ ወይኑ ሲያልቅባቸው
ጥብብ ጭንቅ ሲሉ ማጠፍያው አጥሯቸው
ወይኑ በማለቁ ዳር ይደርሳል ያለው
ተክዟል ዶኪማስ አለሁልህ በለው
ልጄ ወይኑ አለቀ ብለሽ ስትነግሪው
ጌታም በመታዘዝ ልዩ ወይን ሰጣቸው
ብለሽ እንዳማለድሽ ከእፍረት እንዳዳንሽው
ስለእኔም ባዶነት የኔ ጌታ በይው::

  ተጨማሪ ያንብቡ



ሊለካ  የማይችል  ፍቅር
ሊሞት  የማይችል  ሕይወት
ሊደመሰስ  የማይችል  ጽድቅ
ሊረበሽ  የማይችል  ዕረፍት
 ሊጠፋ  የማይችል  ደስታ
 ሊያሳዝን  የማይችል  ተስፋ
ሊቀንስ  የማይችል  ክብር
&l   



የጽዮንን አሥራት ሀገር፣  የቃል ኪዳኑን ታቦት ምድር፤
በቅዱሳን ጸሎት እሳት፣  በነበልባል የምታጥር፤
ለኢትዮጵያ ተስፋ ፈጻሚ፣  የጉንጯን ዕንባ የምታብስ፤
የተዘረጋ የተማጽኖ እጇን፣  በምሕረትህ የምትዳስስ፣
ቅዱስ ሥጋህን ቆርሰህ፣  በክቡር ደምህ የዋጀኸን፤
ሰማያዊ ምስጢርህን ገልጠህ፣  በተዋሕዶ ያከበርከን
ማዕበል ወጀቡን አሻግረህ፣  ከእሥራ ምዕቱ ያደረስከን
የድንግል ማርያም ልጅ፣   ቸሩ መድኃኔ ዓለም ተመስገን ….
                                                ተመስገን …..
     

  



 

የበደለውን አስታውሶ

ያጠፋውን ክሶ

ያለውን ለግሦ

ታዛዥ ለፈጣሪ

  ተጨማሪ ያንብቡ



 ቀሲስ ያሬድ/ገ/መድኀን
ይድረስ ለፈጣሪ መንበረ ጸባዖት
ከትልቁ ሥፍራ ከሰማዩ መንግሥት
ፍርድ ሳይዛነፍ ከሚፈጸምበት፡፡
ላኪው በምድር ላይ ግፍ የደረሰብኝ
ጐስቋላ አገልጋይህ ደካማው ባሪያህ ነኝ፡፡
  ተጨማሪ ያንብቡ


Page 1 of 2First   Previous   [1]  2  Next   Last   

Copyright 2007 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement