ሀ. መዝሙር እግዚአብሔርን በተመስጦ ለማመስገን ለመቀደስ
ለ. መዝሙር ወደ እግዚአብሔር ልባዊ ጸሎት ወይም ልመናን በማራራት ለማቅረብ
ሐ. መዝሙር ለመማሪያና ለማስተማሪያ ወይም ልብን ለማነፅና ነፍስን ለማስደሰት (መንፈስን ለማደስ)፣ ለምክር፣ ለተግሣጽና ደግሞም ለመጽናትና ለማጽናናት እጅግ አድርጎ ይጠቅማል፡፡ መዝሙር ወይም ዜማ የተጀመረው በአራቱ ሰማያት ማለት በሰማያዊት ኢየሩሳሌም በኢዮር፣ በራማና በኤረር ያሉ መላእክት እግዚአብሔር ፈጣሪያቸውን ያለ ዕረፍት ሲያመሰግኑት ነው፡፡ ይህንንም ሲያረጋግጥ ነቢዩ ኢሳይያስ ‹‹እግዚአብሔርን በረጅምና ከፍ ባለ ዙፋን ላይ ተቀምጦ አየሁት፡፡››