View in English alphabet 
 | Monday, September 06, 2010 ..:: ኅብረ ነገር ::.. Register  Login
if ye have word of exhortation for the people, say on

  



ወገብረ ሰላመ በዲበ መስቀሉ
በመስቀሉ ሰላምን አደረገ
 በቀሲስ ስንታየሁ ደምሴ

     መስቀል የሚለው ቃል የተገኘው “ሰቀለ” ከሚለው የግእዝ ቋንቋ ግሥ ነው፡፡ትርጓሜውም “የተመሳቀለ” ወይም “መስቀል” ማለት ነው፡፡

መስቀል ለክርስቲያኖች የሕይወትና የድኅነት ምልክት የሆነው መድኅን ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ከተሰቀለበት ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡
 
 በኦሪት መስቀል የመርገምና የመቀጫ መሣሪያ ሆኖ ይቆጠር ነበር፡፡ ”ማንም ሰው ለሞት የሚያበቃውን ኃጢአት ቢሠራ እንዲሞትም ቢፈረድበት በእንጨትም ላይ ብትሰቅለው በእንጨት ላይ የተሰቀለ በእግዚአብሔር ዘንድ የተረገመ ነውና ሬሳው በእንጨት ላይ አይደር” ዘዳ 21:22-23
 የጥንት ሮማውያን ወንጀለኞችን በመስቀል ተሰቅለው እንዲሞቱ ማድረግ ልማዳቸው ነበር፡፡ክርስቶስ ኢየሱስ ለድኅነተ ዓለም ከመሰቀሉ በፊት የእርግማን ምልክት የነበረው የመስቀል ታሪክ ጌታችን ከተሰቀለበት በኃላ ግን ታሪኩ ተቀይሯል፡፡PDF
  ተጨማሪ ያንብቡ






በቅርቡ ተደርጎ የነበረው የ1999 ዓ.ምሕረቱ የሕዝብ ቆጠራ ከቤተ ክርስቲያናችን አንጻር ስላለው ምንነት የተዘጋጀውን የፍኖተ ሰላም ሬዲዮ ዝግጅት ያዳምጡ።

የሕዝብ ቆጠራው የልዩ ዝግጅታችን አካል የሆነበት ዋነኛው ምክንያት ቆጠራውና ውጤቱ በጉጉት ሲጠበቅ ስለነበርና በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በኩልም የሚኖረው ትርጉም ሰፊ ስለሚሆን ነው።

በጠቅላላው በቆጠራውና በተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ከዲያቆን ኤፍሬም እሸቴ ጋር ቆይታ አድርገናል እንድትከታተሉ እንጋብዛለን።  አስተያየት ወይም ጥያቄ ካለዎት በአድራሻችን ይላኩልን።    




ምክሮች - 1
• የሕይወት መገኛ የሆነውን አምላክህን እወቅ፡፡ በእርሱም ታመን፡፡ እርሱንም ተስፋ አምባና መጠጊያ በማድረግ ኑር፡፡
• ሕይወት ውጣ ውረድ የሚበዛባት ደስታና ሐዘን የሚፈራረቅባት መድረክ በመሆኗ ሁኔታዎችን እንዳመጣጣቸው በትእግሥትና በማስተዋል ለማሳለፍ ተጣጣር፡፡
• በሕይወት ዘመንህ በምታፈራው ገንዘብ የተራበን በማብላት የተጠማን በማጠጣት የታረዘን በማልበስና ችግረኞችን በመርዳት ጽድቅንና መልካም ስምን አትርፍበት፡፡
• ሕይወት በብቸኝነት እጅግ መራራ ናትና በጊዜ ከአምላክህ ጋር ተነጋግረህ የኑሮ ጓደኛህን በመምረጥ በመፈቃቀር በመተሳሰብና በመተጋገዝ ለመኖር ተዘጋጅ፡፡

  ተጨማሪ ያንብቡ


Page 1 of 6First   Previous   [1]  2  3  4  5  6  Next   Last   

Copyright 2007 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement