ሀ/ ማንኛውም ሥራ ወጥና ዘላቂ በሆነ መልኩ ለመሥራት
ማንኛውም ሥራ ወጥና ዘላቂ በሆነ መልኩ ለመሥራት አንድ ሥራ ከየት ተጀምሮ ወዴት እንደሚሄድ የራሱ አካሔድ /ሥርዓት/ ከሌለው አሠራሩ የተዘበራረቀ ይሆንና ፍጻሜው አያምርም፡፡ ሥርዓት የሌለው ሥራም በአግባቡ ሊከወን አይችልም፡፡ ስለሆነም በቤተ ክርስቲያንም የሚፈጸሙ አገልግሎቶች ሁሉ ወጥና አንድ ዓይነት በሆነ ሁኔታ እንዲፈጸሙ ሥርዓት ያስፈልጋቸዋል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም የሥርዓትን አስፈላጊነት ሲገልጥ «ሁሉ በአግባብና በሥርዓት ይህን» ብሏል፡፡1ቆሮ.14÷40፡፡