ማኅበረ ቅዱሳን በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ በእግዚአብሔር ፈቃድ የተጀመረ የኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች መንፈሳዊ እንቅስቃሴ የወለደው ነው፡፡ ለዚህ መንፈሳዊ እንቅስቃሴ መጀመር ቁጥራቸው ከአምስት የማይበልጡ ኦርቶዶክሳውያን ተማሪዎች ምክንያት ከመሆናቸው በቀር በወቅቱ ዛሬ የምናውቀውን ማኅበረ ቅዱሳን ለመመሥረት በሰው የተነደፈ ዓላማና ለዚያ ሲባልም የተሠራ አንድም ተግባር አልነበረም፡፡ ይሁን እንጂ ይህን መንፈሳዊ እንቅስቃሴ ለመጀመር ምክንያት የሆኑ ሁኔታዎች መኖራቸው ግልጥ ነው፡፡ እነዚህም ከዚህ በመቀጠል የሚጠቀሱት ናቸው፡