View in English alphabet 
 | Thursday, May 23, 2013 ..:: መቅድም ::.. Register  Login
if ye have word of exhortation for the people, say on
አማርኛ




ላክ   ተወው
ዜና

በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የሚገኘው የዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ደን በመቃጠሉ መነሾ በሰሜን አሜሪካ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙት ሦስቱ ማኅበራት ማለትም በማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከል፣ በሰሜን አሜሪካ አህጉረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጉባኤ እና ማኅበረ በዓለ ወልድ ባደረጉት ጥሪ እጅግ አስደሳች ምላሽ መገኘቱን በዚህም እስካሁን በጠቅላላው $24,206.52 ዶላር መዋጣቱን የማኅበራቱ ኃላፊዎች ገለፁ።

  ተጨማሪ ያንብቡ


ስብከተ ወንጌል

ማንም ሲፈተን በእግዚአብሔር እፈተናለሁ አይበል
/በቀሲስ ዶ/ር መስፍን ተገኝ/

  


ዜና

በዝቋላ እየተካሄደ ላለው የእሳት ማጥፋት እንቅስቃሴ ርዳታ በማድረግ ላይ ላላችሁ በሙሉ

Zekuala Fireማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከል፣ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጉባኤ እና ማኅበረ በዓለ ወልድ በአንድነት እያስተባበሩት ባሉት እና ዓላማው በአሁኑ ወቅት እሳቱን ለማጥፋት ከየአካባቢው በነቂስ ለወጣው ኢትዮጵያዊ ወገናችን ጉሮሮውን ማርጠቢያ ውኃ፣ ጉልበቱን መደገፊያ ዳቦ ማቅረቢያ እንዲሆን እንዲሁም በገዳሙ ጥሪታቸውን አሟጠው እንግዶቻቸው እሳት ተከላካዮችን  በማስተናገድ  ላሉት ገዳማውያን ርዳታ ማድረግ በሆነው ታላቅ እንቅስቃሴ እስካሁን በፔይፓል (http://zekuala.mahiberekidusan.org/) አካውንታችን (ይህ ጽሑፍ በተዘጋጀበት ወቅት) ሁለት መቶ ሰላሳ ወንድሞች እና እህቶች በዚህ የአጭር ጊዜ አፋጣኝ ጥሪ ምላሽ ሰጥተዋል። ሌሎችም በመለገስ ላይ ይገኛሉ። እናመሰግናለን።

  ተጨማሪ ያንብቡ


ዜና

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

 

በዝቋላ ገዳም እና አካባቢው ደን ላይ የተነሣውን እሳት ለማጥፋት ለሚደረገው ጥረት የግል ልገሳዎን ይስጡ በሚል ሐሳብ በማ/ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከል፣ በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጉባኤ እና በማኅበረ በዓለ ወልድ አስተባባሪነት በሰሜን አሜሪካ የምንገኝ ኦርቶዶክሳውያን አስቸኳይ የገንዘብ ማሰባሰብ ሒደት ላይ እንገኛለን። ዓላማው በአሁኑ ወቅት እሳቱን ለማጥፋት ከየአካባቢው በነቂስ ለወጣው ኢትዮጵያዊ ወገናችን ጉሮሮውን ማርጠቢያ ውኃ፣ ጉልበቱን መደገፊያ ዳቦ ማቅረቢያ እንዲሆን የታሰበ ነው። በባዶ እጁ፣ በቅጠል እና በአፈር ቋያ እሳት ለማጥፋት እየታገለ ላለው ወገን አለኝታነታችንን ለመግለጽ ነው። ስለዚህም በሚከተለው አድራሻ እየገባችሁ የግላችሁን ልገሳ መስጠት የምትችሉ መሆኑን በትህትና እናስታውቃለን።
http://zekuala.mahiberekidusan.org/
  


ትምህርተ ሃይማኖት

ንስሐ የግዕዝ ቃል ሲሆን ትርጉሙ ጸጸት ነው፡፡ ጸጸትነቱ ሰው በሠራው ኃጢአት ተጸጽቶ ኃጢአቱ ይሰረይለት ዘንድ እግዚአብሔርን በሐዘን በለቅሶ ሲለምን እንጂ የጐልማሳ ሚስት ሳልቀማ፣ የሰው ገንዘብ ሳልሰርቅ ቀረሁ … በማለት የሚጸጸተው ጸጸት አይደለም፡፡


ንስሐ ለተጠመቁ ሰዎች ከጥምቀት በኋላ የተሰጠች ሀብት ናት። በጥምቀት ከእግዚአብሔር የምትገኝ የልጅነት ሁለተኛ ማዕረግ ናት፡፡ በሃይማኖት ገንዘብ ያደረግነው የመንግሥተ ሰማያት አራቦን ማለትም መግዣ ናት። ንስሐ ለሚሿት ሰዎች የተከፈተች የይቅርታ በር ናት፡፡ በንስሐ በርነት ከፈጣሪ ወደሚገኝ ቸርነት እንቀርባለን።

ምሥጢረ ንስሐ ማለት አንድ ሰው ከጥምቀት በኋላ የፈጸመውን ጥፋት አውቆ ሁለተኛ ጥፋቱን ላለመድገም ወስኖ በእግዚአብሔርና በካህኑ ፊት ተንበርክኮ ከልቡ ተጸጽቶ ኃጢአቱን በመናዘዝ ከኃጢአቱ እስራት የሚፈታበትና ከእግዚአብሔር ይቅርታን የሚያገኝበት ታላቅ የይቅርታ ምሥጢር ነው።

  ተጨማሪ ያንብቡ


Page 9 of 34First   Previous   4  5  6  7  8  [9]  10  11  12  13  Next   Last   

 የሬድዮ እና ቴሌቪዥን አገልግሎት Minimize

ስብከተ ወንጌልን በሬድዮ እና ቴሌቪዥን የማጠናከር አገልግሎት እናግዝ

ማኅበረ ቅዱሳን የሬድዮ አገልግሎት በዚህ ዓመት መጀመሩ የታወቃል። እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ለረጅም ጊዜ ሲጠበቅ የነበረው የቴሌቪዥን አገልግሎት በየሳምንቱ እሑድ ከ5፡30 እስከ 6፡00 ሰዓት የሚቆይ ተጀምሯል። በኢንተርኔት ላይ http://eotc.tv ድረ ገጽ ላይ መከታተል ይችላሉ። አገልግሎቱን ሁላችንም በጸሎት እንድናስብ እና ለምዕመናን በምንችለው ሁሉ በማድረስ ለአገልግሉቱ ስፋት የበኩላችንን እንድናደርግ በእግዚአብሔር ስም ለማሳሰብ እንወዳለን።

አገልግሎቱን በገንዘብ ለመደገፍ ይህን ገጽ መጠቀም ይችላሉ።


  
 ገዳማትን ይርዱ Minimize

 

Help Monastries


  
 ሶሻል ኔትወርኪንግ

Share |

  
 ግጻዌ


  
Copyright 2007 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement