View in English alphabet 
 | Monday, September 06, 2010 ..:: መቅድም ::.. Register  Login
if ye have word of exhortation for the people, say on
አማርኛ




ላክ   ተወው
ነገረ ቅዱሳን

 

ከመልአከ ሰላም ደጀኔ ሺፈራው
 «አልብኪ ነውር ወኢምንትኒ ላዕሌኪ፤»  መኃ 4:7

የትንቢተ ነቢያት ማረፊያ ፡-የስብከተ ሐዋርያት መነሻ.የሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ምሥጢር ነገረ ማርያም ነው፡፡ ያለ ነገረ ማርያም ነገረ ክርስቶስን መናገር አይቻልም፡፡ በክርስትና ሃይማኖት ታሪክ የተነሡ አያሌ መናፍቃን የመጀመሪያ ችግራቸው የነገረ ማርያምን አማናዊ ትምህርት መቀበል ነበር ፡፡ ያም ችግራቸው ክርስቶስን በትክክል እንዳያምኑት አድርጓቸዋል፡፡ በነገረ ማርያም ላይ የተጣራ ትምህርትና እምነት ቢኖራቸው ኖሮ ለኑፋቄ አይጋለጡም ነበር ፡፡ ንስጥሮስ፡- «አምላክ ወልደ አምላክ» ብሎ በክርስቶስ ለማመን የተሳነው « ወላዲተ አምላክ . ወላዲተ ቃል. እመ እግዚአብሔር » ብሎ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ለማመን በመቸገሩ ነበር፡፡  PDF

  ተጨማሪ ያንብቡ


ነገረ ቅዱሳን

«ብዙኀን ማርያም» እየተሰኘ በየዓመቱ መስከረም ሃያ አንድ ቀን በድምቀት የሚከበረው ይህ በዓል ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን («ወልድ») «ፍጡር» ነው (ሎቱ ስብሐት) ብሎ ያስተማረው የክህደት አስተማሪ የተወገዘበት፣ ሰይጣን ያፈረበት፣ ራሱን በበትረ መስቀል የተቀጠቀጠበት በዓል ነው፡፡

  ተጨማሪ ያንብቡ


ኅብረ ነገር

ወገብረ ሰላመ በዲበ መስቀሉ
በመስቀሉ ሰላምን አደረገ
 በቀሲስ ስንታየሁ ደምሴ

     መስቀል የሚለው ቃል የተገኘው “ሰቀለ” ከሚለው የግእዝ ቋንቋ ግሥ ነው፡፡ትርጓሜውም “የተመሳቀለ” ወይም “መስቀል” ማለት ነው፡፡

መስቀል ለክርስቲያኖች የሕይወትና የድኅነት ምልክት የሆነው መድኅን ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ከተሰቀለበት ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡
 
 በኦሪት መስቀል የመርገምና የመቀጫ መሣሪያ ሆኖ ይቆጠር ነበር፡፡ ”ማንም ሰው ለሞት የሚያበቃውን ኃጢአት ቢሠራ እንዲሞትም ቢፈረድበት በእንጨትም ላይ ብትሰቅለው በእንጨት ላይ የተሰቀለ በእግዚአብሔር ዘንድ የተረገመ ነውና ሬሳው በእንጨት ላይ አይደር” ዘዳ 21:22-23
 የጥንት ሮማውያን ወንጀለኞችን በመስቀል ተሰቅለው እንዲሞቱ ማድረግ ልማዳቸው ነበር፡፡ክርስቶስ ኢየሱስ ለድኅነተ ዓለም ከመሰቀሉ በፊት የእርግማን ምልክት የነበረው የመስቀል ታሪክ ጌታችን ከተሰቀለበት በኃላ ግን ታሪኩ ተቀይሯል፡፡PDF
  ተጨማሪ ያንብቡ



የዲሲ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ቃለ ምዕዳን እና ቡራኬ አስተላለፉ፡፡

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ አሜን፡፡
በአለንበት አገር በሰሜን አሜሪካ፤ በሀገራችን በኢትዮጵያና በልዩ ልዩ አኅጉራት የምትገኙ አባቶቼና እናቶቼ ወንድሞቼና እኅቶቼ …
ተጨማሪ

  



ይህ ስለ ማኀበረ ቅዱሳን ማንነትና አገልግሎት የሚያስተነትነው ሦስተኛ ሣምንት ልዩ መርሐ ግብራችን ነው። በዚህ ዝግጅታችን ሁለት የማኀበሩ አባላትን እናቀርብላችኋለን። እንግዶቻችን በማኀበሩ ውስጥ ለረዥም ጊዜ በተለያዩ የአገልግሎት ሥፍራዎች ያገለገሉት መምህር ብርሃኑ ጎበና እና ዲያቆን ኤፍሬም እሸቴ ይሆናሉ።
ባለፉት ሁለት እሑዶች (8/23/2009 እና 8/30/2009) በተላለፉ የሀገር ፍቅር ሬዲዮ ዝግጅቶች አባ ኃ/ሚካኤል ወልደ ተ/ሃይማኖት የተባሉ ግለሰብ የማኀበረ ቅዱሳንን መልካም አገልግሎትና ስም የሚያጠቁር ቃለ ምልልስ ማድረጋቸውና እኛም ለዚያ መልስ የሚሆን አንድ ዝግጅት ማቅረባችን ይታወሳል። ግለሰቡ በዋነኝነት ያነሷቸውን ተጨማሪ ነጥቦች መነሻ በማድረግ ይህንን ቀጣይ ዝግጅት እናቀርባለን። እንደ መልካም የቤተ ክርስቲያን አገልጋይና ኦርቶዶክሳዊ አባት በመምሰል፣ ሳይላኩ እንደተላኩ፣ ሥልጣን ሳይኖራቸው እንደባለ ሥልጣን፣ ከተመደቡበት ሥፍራ ጠፍተው መጥተው ሳለ ልክ ተሹመው እንደመጡ በማሰመሰል በውጪ ሀገር (በዳያስጶራ) ያለውን ምእመን ለማሳሳት በመሞከር ላይ ያሉትን የእኒህን ሰው ማንነትና ግብር በምንመለከትበት በዚህ ዝግጅት የተለያዩ ጥያቄዎችን ለእንግዶቻችን በማቅረብ በጥልቀት እንወያያለን።

መልካም ጊዜ።

  


Page 9 of 24First   Previous   4  5  6  7  8  [9]  10  11  12  13  Next   Last   

 ፌስ ቡክ


  
 ገዳማትን ይርዱ Minimize

 

Help Monastries


  
 ግጻዌ


  
Copyright 2007 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement