|
ቅዱሳን መላእክት
ቅዱሳን መላእክት በእግዚአብሔርና በሰው መካከል ለአገልግሎት የሚፋጠኑ ናቸው፡፡ ከእግዚአብሔር ዘንድ ምሕረትንና ቸርነትን ወደ ሰው ልጆች፣ የሰዎችንም ጸሎትና ልመና ወደ እግዚአብሔር የሚያደርሱ ናቸው፡፡
ቅዱሳን መላእክት በመንገዳችን ሁሉ እንደሚጠብቁን ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት ሲያስረዳ እንዲህ ብሏል #በመንገድ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንነተ ያዝዛቸዋልና፣ እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል$ (መዝ. 90/91/-11)፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
ቅዱሳን መላእክት
መስገድ የሚለው ቃል መዋረድ፣ ማጐንበስ፣ መንበርከክ፣ መደፋት፣ በግንባር መውደቅ፣ ግንባርን ምድር አስነክቶ መሬት ስሞ መመለስ ነው በማለት የአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ያትታል፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን ስግደት የአምልኮና የጸጋ ተብሎ ይከፈላል፡፡ የአምልኮ ስግደት ለእግዚአብሔር ብቻ የሚቀርብ ሲሆን የጸጋ ስግደት ደግሞ እግዚአብሔር ላከበራቸው ቅዱሳን ሰዎችና መላእክት የሚቀርብ ነው፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
ክርስቲያናዊ ሕይወት
የእግዚአብሔርን ስም በከንቱ መጥራት ሲባል ምን ማለት ነው? የአምላካችን የእግዚአብሔር ስም የከበረ በመሆኑ እንደተገኘ የሚጠሩት፣ እንደአጋጠመ የሚናገሩት አይደለም፡፡ ይልቁንም በመፍራትና በመንቀጥቀጥ በትሕትና ሆነው ሊጠሩት የሚገባ ክቡር ስም ነው፡፡ ይሁን እንጂ አንዳንድ ሰዎች የእግዚአብሔርን ስም ያለአግባብ በነገራቸው ሁሉ ውስጥ ሲያስገቡት፣ ሥፍራም ጊዜም ሳይመርጡ እንደፈለጉት ሲጠሩት ይስተዋላሉ፡፡ እንደዚህ ዓይነት ሰዎች እምነትና ፊሪሃ እግዚአብሔር አላቸው ለማለት አያስደፍርም፤ ምክንያቱም የሚያምኑና
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
ዜና
በ1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር የተገነባው ቤተክርስቲያን ተመረቀ፡፡
የጋምቤላ ሕዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድርን ጨምሮ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮምሽነርና የካቢኔ ጉዳዮች ጽ/ቤት ሓላፊ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን እምነት ተቀብለው ተጠመቁ፡፡ በጋምቤላ ሀገረ ስብከት በአንድ ነጥብ ስምንት ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባው የደብረ መድኃኒት ቅድስት ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ተጠናቆ ቅዳሴ ቤቱም ተከብሯል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
ዜና
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በደብረ ወልደ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ እና በመካነ ጎለጎታ ቅድስት ማርያም ጠበል ሰሞኑን ከአንዲት እኅት ከሆዷ ጥቁር ወፍ ወጣላት፡፡ በክርስትና ስሟ መንበረ ማርያም ተብላ የምትጠራው እኅት ለ20 ዓመታት ያህል በሆድ ሕመማት ስትሰቃይ መቆየቷን የምትናገረው መንበረ ማርያም፤ ስቃይዋን በዘመናዊው ሕክምና ለማስታገስ ያልሔደችበት ቦታና ያልወሰደችው መድኃኒት የለም፡፡ ይሁንና የምትወስደው ሕክምና ለጊዜው ስቃይዋን ከማስታገስ በስተቀር ከሕመሟ ልትድን ባለመቻሏ ከዚህ በኋላ ይግደለኝ እንጂ ሕክም ናም ሆነ መድኃኒት መጠቀም የለብኝም፤ ብላ ጠበል ለመጠመቅ እንደ ወሰነች ትናገራለች፡፡ በውሳኔዋም መሠ ረት ወደ ወልደ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን ጠበል በመሄድ ስትጠመቅ በላይዋ ላይ የሰፈሩ 681 አጋንንት እንዳሉ በላይዋ ላይ ያደሩት የሰይጣን ሠራዊት ለፍልፎ በጥቁር ወፍ አምሳል ከሆዷ ውስጥ ሊወጣላት ችሏል፡፡ ምእመናን በዕለቱ ከሆዷ ውስጥ በትውከትነት እንደ ጥይት ተወርውሮ የወጣውን ጥቁር ወፍ ከነሕይወቱ በማየት በቪዲዮ በመቅረጽ የእግዚአብሔርን ድንቅ ተአምር እንደ መሰከሩ ተገልጿል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
|