View in English alphabet 
 | Monday, September 06, 2010 ..:: መቅድም ::.. Register  Login
if ye have word of exhortation for the people, say on
አማርኛ




ላክ   ተወው
ዜና

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኀበረ ቅዱሳን ጥር 22 እና 23 2002 ዓ.ም በሎስ አንጀለስ ያቀረበው ዐውደ ርእይ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን የዝግጅቱ አስተባባሪዎች አስታወቁ:: ቅዳሜ ጥር 22 ቀን 2002 ዓ.ም ከጠዋቱ አራት ሰዓት ላይ ከሎስ አንጀለስ ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን፣ ከላስ ቬጋስ ቅዱስ ሚካኤል ወቅድስት ኪዳነ ምሕረት እንዲሁም ከፖርትላንድ በተጋበዙ ቆሞሳትና ቀሳውስት በጸሎት ከተከፈተ ጊዜ ጀምሮ ለሁለት ቀናት በቆየው በዚሁ ዐውደ ርእይ ላይ በመቶዎች የሚቆጠሩ እንግሊዘኛ ተናጋሪዎች እንዲሁም ኢትዮጵያውያን መመልከት እንደቻሉ ታውቋል::

  ተጨማሪ ያንብቡ


ስብከተ ወንጌል

 

ሕዝ 347
                      መምህር ዕርገተ ቃል ይልማ

ከዐበይት ነቢያት አንዱ የሆነው ሕዝቅኤል ከጌታ ልደት 597 ዓመት በፊት የተነሳ ነቢይ ነው፡፡ይህ ታላቅ ነቢይ የእሥራኤል ልጆች ወደ ባቢሎን ተማርከው በስደት በሄዱ ጊዜ

ከምርኮኞች አንዱ በመሆን እስራኤላውያን የደረሰባቸውን መከራና ስቃይ በዐይኑ ለማየት ጩኸታቸውንም በጆሮው ለመስማት ችሏል፡፡ ኢየሩሳሌም ለከፋ ውድቀት ከመዳረጓ በፊት ሕዝቡ ራሳቸውን በንስሐ ወደ እግዚአብሔር እነዲያቀርቡ መክሯል፡፡ይሁን እንጂ ከበደላቸውና ከኃጢአታቸው ተመልሰው በጽድቅ መንገድ ሊጓዙ ስላልቻሉ የተለያየ መከራ ደረሶባቸዋል፡፡

  ተጨማሪ ያንብቡ


ኅብረ ነገር

“እርሱ ስለ እኛ ነፍሱን አሳልፎ ሰጥቶአልና በዚህ ፍቅርን ዐውቀናል፡፡ እኛም ስለ ወንድሞቻችን ነፍሳችንን አሳልፈን እንድንሰጥ ይገባናል›› (1 ዮሐ 3፡16)
በዓለማችን ላይ በተለያዩ አጋጣሚዎች ታላላቅ የኪነ ጥበብ ሰዎች፣ የታወቁ ፈላስፎች ስለ ፍቅር ብዙ ብለዋል፡፡ ይሁን እንጂ የእውነተኛውን ፍቅር ምንነቱን የገለጹት፤ በተግባርም ያዋሉት በጣም ጥቂቶች ናቸው፡፡

  ተጨማሪ ያንብቡ


ቅዱሳን መላእክት

(ከብርሃኑ ጎበና)
ቅዱስ ማለት የተለየ፣ የተከበረ፣ የተመሰገነ፣ የተመረጠ ማለት ነው፡፡ ቅዱሳን መላእክት ስንልም የተመሰገኑ፣ ከርኵሳን መላእክት የተለዩ፣ ክቡራን መላእክት ማለታችን ነው፡፡ መላእክት ሁለት ወገን ናቸው፡፡ ብርሃናውያን መላእክትና የጨለማ አበጋዝ የሆነው የዲያብሎስ ሠራዊት የሆኑት እኩያን መላእክት፡፡ ስለዚህ የእግዚአብሔርን መላእክት ከሌሎቹ መላእክት በአጠራር የምንለያቸው ቅዱስ በሚል ቅጽል ነው፡፡
  ተጨማሪ ያንብቡ


ቅዱሳን መላእክት

የመላእክት መላእክት በአፈጣጠራቸው ረቂቃን መናፍስት በመሆናቸው እንደ ሥጋ ለባሽ ፍጥረታት አይበሉም፣ አይጠጡም፣ አያገቡም (ማቴ 22$30፡፡ ሉቃ 24$39)፡፡ ጾታም የላቸውም፡፡ አንዳንድ ሰዎች ግን መላእክት በአንድ ወቅት ከሰው ልጆች ጋር እንደወደቁ አድርገው ይናገራሉ፡፡ ለዚህም መረጃ አድርገው ለማቅረብ የሚሞክሩት ‹‹የእግዚአብሔር ልጆች የሰውን ሴቶች ልጆች አገቡ›› የሚለውን ኃይለ ቃል ነው (ዘፍ.6$2)፡፡
  ተጨማሪ ያንብቡ


Page 7 of 24First   Previous   2  3  4  5  6  [7]  8  9  10  11  Next   Last   

 ፌስ ቡክ


  
 ገዳማትን ይርዱ Minimize

 

Help Monastries


  
 ግጻዌ


  
Copyright 2007 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement