|
ዜና
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኀበረ ቅዱሳን ጥር 22 እና 23 2002 ዓ.ም በሎስ አንጀለስ ያቀረበው ዐውደ ርእይ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን የዝግጅቱ አስተባባሪዎች አስታወቁ:: ቅዳሜ ጥር 22 ቀን 2002 ዓ.ም ከጠዋቱ አራት ሰዓት ላይ ከሎስ አንጀለስ ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን፣ ከላስ ቬጋስ ቅዱስ ሚካኤል ወቅድስት ኪዳነ ምሕረት እንዲሁም ከፖርትላንድ በተጋበዙ ቆሞሳትና ቀሳውስት በጸሎት ከተከፈተ ጊዜ ጀምሮ ለሁለት ቀናት በቆየው በዚሁ ዐውደ ርእይ ላይ በመቶዎች የሚቆጠሩ እንግሊዘኛ ተናጋሪዎች እንዲሁም ኢትዮጵያውያን መመልከት እንደቻሉ ታውቋል::
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
ስብከተ ወንጌል
ሕዝ 34፡7
መምህር ዕርገተ ቃል ይልማ
ከዐበይት ነቢያት አንዱ የሆነው ሕዝቅኤል ከጌታ ልደት 597 ዓመት በፊት የተነሳ ነቢይ ነው፡፡ይህ ታላቅ ነቢይ የእሥራኤል ልጆች ወደ ባቢሎን ተማርከው በስደት በሄዱ ጊዜ
ከምርኮኞች አንዱ በመሆን እስራኤላውያን የደረሰባቸውን መከራና ስቃይ በዐይኑ ለማየት ጩኸታቸውንም በጆሮው ለመስማት ችሏል፡፡ ኢየሩሳሌም ለከፋ ውድቀት ከመዳረጓ በፊት ሕዝቡ ራሳቸውን በንስሐ ወደ እግዚአብሔር እነዲያቀርቡ መክሯል፡፡ይሁን እንጂ ከበደላቸውና ከኃጢአታቸው ተመልሰው በጽድቅ መንገድ ሊጓዙ ስላልቻሉ የተለያየ መከራ ደረሶባቸዋል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
ኅብረ ነገር
“እርሱ ስለ እኛ ነፍሱን አሳልፎ ሰጥቶአልና በዚህ ፍቅርን ዐውቀናል፡፡ እኛም ስለ ወንድሞቻችን ነፍሳችንን አሳልፈን እንድንሰጥ ይገባናል›› (1 ዮሐ 3፡16)
በዓለማችን ላይ በተለያዩ አጋጣሚዎች ታላላቅ የኪነ ጥበብ ሰዎች፣ የታወቁ ፈላስፎች ስለ ፍቅር ብዙ ብለዋል፡፡ ይሁን እንጂ የእውነተኛውን ፍቅር ምንነቱን የገለጹት፤ በተግባርም ያዋሉት በጣም ጥቂቶች ናቸው፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
ቅዱሳን መላእክት
(ከብርሃኑ ጎበና)
ቅዱስ ማለት የተለየ፣ የተከበረ፣ የተመሰገነ፣ የተመረጠ ማለት ነው፡፡ ቅዱሳን መላእክት ስንልም የተመሰገኑ፣ ከርኵሳን መላእክት የተለዩ፣ ክቡራን መላእክት ማለታችን ነው፡፡ መላእክት ሁለት ወገን ናቸው፡፡ ብርሃናውያን መላእክትና የጨለማ አበጋዝ የሆነው የዲያብሎስ ሠራዊት የሆኑት እኩያን መላእክት፡፡ ስለዚህ የእግዚአብሔርን መላእክት ከሌሎቹ መላእክት በአጠራር የምንለያቸው ቅዱስ በሚል ቅጽል ነው፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
ቅዱሳን መላእክት
የመላእክት መላእክት በአፈጣጠራቸው ረቂቃን መናፍስት በመሆናቸው እንደ ሥጋ ለባሽ ፍጥረታት አይበሉም፣ አይጠጡም፣ አያገቡም (ማቴ 22$30፡፡ ሉቃ 24$39)፡፡ ጾታም የላቸውም፡፡ አንዳንድ ሰዎች ግን መላእክት በአንድ ወቅት ከሰው ልጆች ጋር እንደወደቁ አድርገው ይናገራሉ፡፡ ለዚህም መረጃ አድርገው ለማቅረብ የሚሞክሩት ‹‹የእግዚአብሔር ልጆች የሰውን ሴቶች ልጆች አገቡ›› የሚለውን ኃይለ ቃል ነው (ዘፍ.6$2)፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
|