View in English alphabet 
 | Monday, September 06, 2010 ..:: መቅድም ::.. Register  Login
if ye have word of exhortation for the people, say on
አማርኛ




ላክ   ተወው
ዜና

የከምባታ፣ ሐድያ፣ ጉራጌና ስልጢ አህጉረ ስብከተ ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የነበሩት ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ ዐረፉ፡፡
ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ በደረሰባቸው ሕመም ሳቢያ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ሰኔ 13 ቀን 2002 ዓ.ም ዐርፈዋል፡፡

ሥርዓተ ቀብራቸው ሰኔ 15 ቀን 2002 ዓ.ም ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ ካህናት አባቶችና ምእመናን በተገኙበት በምሁር ኢየሱስ ገዳም ተፈጽሟል፡፡ ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ ያስተዳድሩት በነበረው ሀገረ ስብከት ውስጥ በሚገኘው እዣና ወለኔ ወረዳ /ምሁር ኢየሱስ ገዳም አካባቢ/ ከአባታቸው ከመምሬ ክንፈ ሚካኤልና ከእናታቸው ከወ/ሮ አስካለ ማርያም በ1951 ዓ.ም ተወለዱ፡፡ ዕድሜያቸው ለትምህርት እንደደረሰ የምሁር ኢየሱስ ገዳም ቄሰ ገበዝ የነበሩት አባታችው በዚያው ፊደልና የቁጥር ትምህርት አስተማሯቸው፡፡

  ተጨማሪ ያንብቡ


ቅዱሳን መላእክት

 የቅዱስ ሚካኤል ስሞች
መላእክት ቁጥራቸው እጅግ ብዙ ቢሆንም በ99 ነገድ የተከፈሉና አለቆችም ያሏቸው ናቸው፡፡ የእነዚህ ሁሉ መላእክት አለቃ የሆነው ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡ በትህትናው ልዕልናን ያገኘው ቅዱስ ሚካኤል በእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠው ክብር ከማንኛውም መልአክ የበለጠ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ አስቀምጦታል፡፡

  ተጨማሪ ያንብቡ



 

በኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤት ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከል 12ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን  በዳላስ ቴክሳስ ከግንቦት 20-22/2002 ዓ.ም አካሄደ። ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ የሰሜን ምዕራብ አሜሪካ የካሊፎርኒያ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ከተለያዩ ግዛቶች የመጡ ካህናት አባቶች፣ ወንድሞች ዲያቆናት፣ በጠቅላላው በአሜሪካ የሚገኙ የማ/ቅዱሳን አባላት እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት የተካሄደው ይህ ዓመታዊ ጉባዔ ዓመታዊ ሪፖርቶችን ከመስማቱም ባሻገር የ2003 ዓ.ም የማዕከሉ ዕቅድ ላይ ተወያይቷል።

  ተጨማሪ ያንብቡ



  



(በአባ ዘሚካኤል ዼሬሣ)

ነቢዩ ነህምያ በባቢሎን በሱሳ ግንብ ሳለ፤ ከወንድሞቹ አንዱ አናኒና ሌሎች ከይሁዳ መጡ፡፡ ነቢዩ ነህምያም በይሁዳ ስላሉ ከምርኮ ስለተረፉትና ስለኢየሩሳሌም ከተማ ጠየቃቸው፡፡ እነርሱም እንዲህ አሉት «'ከምርኮ የተረፉት በታላቅ መከራና ስድብ አሉ፡፡ የኢየሩሳሌም ቅጥር ፈርሶአል፡፡ በሮችዋም በእሳት ተቃጥለዋል»፡፡ ይህንን በሰማ ጊዜ ነህምያ ታላቅ የሆነ ሐዘኑን እንደሚከተለው ገለጸ፡፡

«ይህንን ቃል በሰማሁ ጊዜ ተቀምጬ አለቀስሁ፤ አያሌ ቀንም አዝን ነበር፡፡ በሰማይ አምላክ ፊት እጾምና እጸልይ ነበር፡፡... ቃል ኪዳን ምሕረትን የምትጠብቅ ታላቅና የተፈራህ አምላክ ሆይ... የምጸልየውን ጸሎት ትሰማ ዘንድ ጆሮህ ያድምጥ፣ ዐይኖችህም ይከፈቱ፤ በአንተ ላይም ያደረግነውን የእስራኤልን ልጆች ኃጢአት እናዘዝልሃለሁ፤ እኔና የአባቴም ቤት በድለናል፡፡ እጅግ ክፉ ሠርተናል ለባሪያህም ለሙሴ ያዘዝከውን ሕግና ሥርዐት አልጠበቅንም፡፡» (ነህ. 1፣ 4-8)፡፡

  ተጨማሪ ያንብቡ


Page 2 of 24First   Previous   1  [2]  3  4  5  6  7  8  9  10  Next   Last   

 ፌስ ቡክ


  
 ገዳማትን ይርዱ Minimize

 

Help Monastries


  
 ግጻዌ


  
Copyright 2007 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement