View in English alphabet 
 | Friday, May 18, 2012 ..:: መቅድም ::.. Register  Login
if ye have word of exhortation for the people, say on
አማርኛ




ላክ   ተወው
ንቁ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

“ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል የሚያካሒዱት ሕገ ቤተ ክርስቲያንን የጣሰ እንቅስቃሴ ይቁም”
(በማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከል ጽ/ቤት) (To read in PDF
)

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን  የሰሜን አሜሪካ ማዕከል ተዋቅሮ  አገልግሎቱን ሲፈጽም እነሆ 14 ዓመታትን አስቆጥሯል:: በነዚህም ዓመታት በቅዱስ ሲኖዶስ በተሰጠው መመሪያ መሠረት:-
1.  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን እምነትና ሥርዓት እንዲስፋፋ፣
2.  የቤተ ክርስቲያን ሕግና ሥርዓት  እንዲከበር፣
3. ከአጥቢያ  ቤተ ክርስቲያን እስከ አኅጉረ ስብከት ያለው የቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅር እንዲደራጅና እንዲጠናከር በማድረግ፣
4.  የሕዝበ ክርስቲያኑ አንድነት እንዲጠበቅና ማኅበራዊ ሕይወት እንዲጠናከር፣
5.  ወጣቱ በሰንበት ት/ቤትና በሰባካ ጉባኤ ገብቶ በንቃትና በባለቤትነት እንዲሳተፍ፣
6. አባቶች በአስተዳደር ምክንያት ቢለያዩም ይህን ችግራቸውን በጠረጴዛ ዙርያ በመመካከር በእርቅ አንድነታቸውን እንዲቀጥሉና  እንዲያጠናክሩ በማድረግ ለእርቅ የተቻለውን ድጋፍ በማድረግ የበኩሉን ጥረት አድርጓል::

  ተጨማሪ ያንብቡ


ነገረ ቅዱሳን

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

ዮም ፍስሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም


«መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው» /መዝ. ፹፮፥፩/

በትራክት መልክ የተዘጋጀውን መልእክት ለማግኘት እዚህ ይጫኑ
Click here to find the message about the Nativity of our Lady
  ተጨማሪ ያንብቡ


ማኅበረ ቅዱሳን

ማሩ አይምረር፤ ወተቱ አይጥቆር

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ

“ማኅበረ ቅዱሳን”

ሚያዚያ 24/2004 ዓ.ም.

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሥር ተዋቅሮ መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኘው ማኅበረ ቅዱሳን በእግዚአብሔር ፈቃድ አገልግሎቱን ከጀመረ እነሆ ሃያ ዓመታት ተቆጠሩ። ምንም እንኳን ማኅበሩን በራሳቸው ፈቃደኝነት የተሰባሰቡ ኦርቶዶክሳውያን ቢመሠርቱትም የማኅበሩ መሠረታዊ ዓላማ ግን ቤተ ክርስቲያን ተልእኮዋን ለማሳካት በምታከናውናቸው ተግባራት የልጅነት ድርሻውን ለመወጣት በመሆኑ ወደ ቤተ ክርስቲያን መዋቅር በመግባት መተዳደሪያ ደንቡ በቅዱስ ሲኖዶስ ጸድቆ በተቀመጠለት ተግባርና ሓላፊነት መሠረት አገልግሎቱን እያከናወነ ያለ ማኅበር ነው። አባላቱም በሀገር ውስጥም ሆነ በውጪ ሀገራት በቤተ ክርስቲያኗ አጥቢያዎች በሚገኙ ሰበካ ጉባኤያት እና ሰንበት ት/ቤቶች ተመዝግበው የሚጠበቅባቸውን ክርስቲያናዊ ግዴታ እየተወጡ ይገኛሉ። እነዚህ አባላት አብዛኛዎቹ ቤተ ክርስቲያናቸውን በገንዘብ፣ በዕውቀትና በጉልበት ለማገልገል በፈቃዳቸው ቃል የገቡ ቤተ ክርስቲያንና ሀገሪቷ ካሏት ልዩ ልዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተመርቀው ቤተ ክርስቲያናቸውን አገራቸውንና ወገናቸውን በልዩ ልዩ ሙያ እያገለገሉ የሚገኙ ናቸው።
ተጨማሪ ያንብቡ
  


ኅብረ ነገር

 
“እምነ ጽዮን ይብል ሰብእ ወብእሲ ተወልደ በውስቴታ ወውእቱ ልዑል ሣረራ"
  ተጨማሪ ያንብቡ


ስብከተ ወንጌል

ትንሣኤ (በመልአከ ሰላም ቀሲስ ያሬድ ገ/መድኅን)

በአርዓያ ሥላሴ የተፈጠረው አዳም

አጋዕዝተ ዓለም ሥላሴ ፍጥረታትን ለተከታታይ አምስት ቀናት ከፈጠሩ በኋላ በስድስተኛው ቀን /ዓርብ/ በነግህ እንዲህ አሉ።  ‹‹ንግበር ሰብአ በአርዓያነ ወበአምሳሊነ፤ ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌያችን እንፍጠር›› /ዘፍ ፩፥፳፮/።  ሥላሴ በመልካችን እንደ ምሳሌያችን ማለታቸው እንዴት ነው ቢሉ ሥላሴ ለባውያን፣  ነባብያን፣  ሕያዋን ናቸው።  አዳምም ለባዊ፣  ነባቢ፣  ሕያው ነው።  ሥላሴ ፍጹም መልክእ እንዳላቸው አዳምም ፍጹም መልክእ  አለው።  ሥላሴ በልብ በቃል፣  በእስትንፋስ ይመሰላሉ ለሰውም ልብ፣  ቃል፣  እስትንፋስ አለው። ሥላሴ በባሕርያቸው የሚገዙትን አዳም በጸጋ እንዲገዛ ሥልጣን ሰጥተውታል።

  ተጨማሪ ያንብቡ


Page 1 of 29First   Previous   [1]  2  3  4  5  6  7  8  9  10  Next   Last   

 ማስታወቂያ Minimize


  
 ማስታወቂያ Minimize


  
 ገዳማትን ይርዱ Minimize

 

Help Monastries


  
 ሶሻል ኔትወርኪንግ

Share |

  
 ግጻዌ


  
Copyright 2007 by Mahibere Kidusan USA Center  | Terms Of Use | Privacy Statement