|
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፤ ሐዋርያዊ ተልእኮዋን የምታስፈጽምበት፣ የውስጥም ሆነ የውጪ ዘርፈ ብዙ መንፈሳዊ አገልግሎቷን በአግባቡ የምታቀናጅ በትና የምታከናውንበት፣ ማዕከላዊውን የቤተ ክርስቲያኒቱን ልዕልናና
የሥልጣን እርከን ተዋረድ ጠብቃ ራሷን የምትመራበትና የምትገለገልበት የአስተዳደር ሥርዓት ባለቤት ናት፡፡
አስገኝዋ እግዚአብሔር በመሆኑ የመንፈሳዊ አስተዳደር ሥርዓቷም እግዚአብሔር ነው፡፡ ለዚህም በዓለመ መላእክት የነገደ መላእክትን የሥ ልጣን እርከን፣ የአገልግሎት ስምሪትና አሠፋፈር፤ የእግዚአብሔር ሰዎች በሕገ ልቡና የተመሩበት፤ ከዚያም በሕገ ኦሪትና በሕገ ወንጌል እስከ አሁን የተደረሰበት የአስ ተዳደር ሥርዓትና አፈጻጸም ለአብ ነት የሚጠቀስ ነው፡፡ 
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
ነገረ ቅዱሳን
ቤተ ክርስቲያናችን ለምን ስለ እመቤታችን ዘወትር እንደምታስተምር አንዳንድ ሰዎች ግር ሲላቸው ይታያል፡፡ እንዲያውም ‹‹አላዋቂ ሳሚ...›› እንዲሉ ስለ እመቤታችን ማስተማå ስለ ጌታችን እንዳታስተምር አድርጓታል ብለው የሚናገሩም አሉ፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን ግን ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የምታስተምረው ለርሷ ካላት ልዩ ፍቅር ብቻ ወይም ስለጌታችን የምታስተምረው ለርሷ ካላት ልዩ ፍቅር ብቻ ወይም ስለጌታችን የምታስተምረው አልቆባት አይደለም፡፡ ምክንያቱም ከኢትዮጵያ ሊቃውንት በላይ ለነገረ መለኰት ምሁርና ጥንቁቅ ከማግኘት የሰማይን ስፋት ልክ ማግኘቱ ሳይቀል አይቀርም፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
ቅዱሳን መላእክት
የቅዱስ ሚካኤል ስሞች
መላእክት ቁጥራቸው እጅግ ብዙ ቢሆንም በ99 ነገድ የተከፈሉና አለቆችም ያሏቸው ናቸው፡፡ የእነዚህ ሁሉ መላእክት አለቃ የሆነው ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡ በትህትናው ልዕልናን ያገኘው ቅዱስ ሚካኤል በእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠው ክብር ከማንኛውም መልአክ የበለጠ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ አስቀምጦታል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
ዜና
በጀርመን ፍራንክፈርት የተካሄደው ዐውደ ርዕይ ተጠናቀቀ
በማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል መዝሙርና ሥነ ጥበባት ክፍል
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትላንት ዛሬና ነገ በሚል ርዕስ ከግንቦት 21 እስከ 24 ቀን 2001 ዓ.ም በፍራንክፈርት ከተማ ተዘጋጅቶ የነበረው ዐውደ ርዕይ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ።
በማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል ጀርመን ቀጠና ማእከል ተዘጋጅቶ በፍራንክፈር ኢኮነን ሙዚየም የቀረበውን ይህንን ዐውደ ርዕይ መርቀው የከፈቱት ብፁዕ አቡነ እንጦንስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ናቸው።
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
በማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከል 11ኛ ዓመታዊ ጉባዔ ተካሄደ
በኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማ/መምሪያ ሥር አገልግሎቱን በመስጠት ላይ የሚገኘው ማኅበረ ቅዱሳን በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ ሆኖ ካዋቀራቸው ማዕከላት አንዱ የሆነው የአሜሪካ ማዕከል 11ኛ ዓመታዊ ጉባዔውን በዋሺንግተን ዲሲ ከተማ አካሄደ፡፡
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የዋሺንግተን ዲሲና የኒውዮርክ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ አበው ካህናትና በአሜሪካ የሚገኙ አባላት እንዲሁም የዋናው ማዕከል ተወካይ የሆኑት ቀሲስ ዶ/ር ሰሙ ምትኩ የተገኙበት ይህ ጉባዔ ግንቦት 15 እና 16/2001 ዓ.ም (ሜይ 23 እና 24/2009) የተገኙበት ይህ ታላቅ ጉባዔ ከግንቦት 2000 እስከ ግንቦት 2001 ዓ.ም ያለውን የሥራ ሪፖርት ከማዳመጡም በላይ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመወያየት ውሳኔዎችን አሳልፏል። ፎቶዎችን ይመልከቱ
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
ትምህርተ ሃይማኖት
የጾም ወቅት መንፈሳዊ ተጋድሎዎች የሚበዙበት፣ ለእግዚአብሔር ያለንን ፍቅር የምንገልጥበት፣ እምነታችን የሚጠነክርበት፣ ከዲያብሎስ ጋራ የምንዋጋበት፣ ከእግዚአብሔር ጋር ያለንን ቅርበትና ቤተሰባዊነት የምናሻሽልበት፣ ምሥጢራችንን ለአምላካችን የምንናገርበት፣ ድሆችን የምናስብበት ጊዜ ነው፡፡ ስለዚህም የሚጾም ሁሉ በሥጋ ፈቃዱ ላይ ድል ይቀዳጃል፣ የለመነውን ያገኛል፣ ሰማያዊ የሆነውን ምሥጢር ለማየት ከዓላማዊ ነገሮች ተለይቶ ይነጠቃል፣ በዓለም እየኖረ ከዓለሙ ይለያል፡፡ ዮሐ.15÷19፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
በኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማ/ምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከል በዚህ የዕቅድ ዓመት ሲያካሒዳቸው የነበሩትን ተጓዥ ዐውደ ርእዮች ማጠናቀቁን የማዕከሉ ጽ/ቤት አስታወቀ።
“የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ትናንት ዛሬ ነገ” በሚል ርዕስ እና “ለቤተ ክርስቲያን አንድነት በአንድነት እንሥራ” በሚል መሪ ቃል በ ሰባት ከተሞች የቀረበው ይኸው ዝግጅት 11 ክፍሎች ሲኖሩት አንድ ሰው ገብቶ እስኪወጣ ከሁለት ሰዓታት ላላነሰ ጊዜ በገለጻ የተሞሉ ከ115 በላይ ፖስተሮችንና ሎሎች ዝግጅቶችን የሚመለከትበት ትልቅ ትዕይንት ነበር። የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ፣ ቅ/መካናት፣ ቅ/ መጻሕፍት፣ ቅ/ ሥዕላት፣ ዜማ፣ ንዋያተ ቅድሳት፣ የኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር፣ የቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ፈተናዎች፣ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በዳያስጶራ፣ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ነገ እንዲሁም በመጨረሻ ማኅበረ ቅዱሳን በሚሉ ርእሶች የተዋቀረው ይህ ዝግጅት ለዕይታ በበቃባቸው ከተሞች በሙሉ አስተማሪ ሆኖ ማለፉ ታውቋል።
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
‹በአዳም ባህርይ ውስጥ የምታበራ ነጭ ዕንቁ› ቅዱስ ያሬድ
ቅዱስ ያሬድ ስለእመቤታችን ድንግል ማርያም በድጓው ‹ማርያም ተሐቱ እምትካት ውስተ ከርሱ ለአዳም ከመ ባሕርይ ጸአዳ፣ ማርያምስ ከጥንት ጀምሮ በአዳም ባሕርይ እንደ ነጭ ዕንቁ ታበራለችና› ጀምሮ በተመረጡና በተቀደሱ አባቶችና እናቶች በጥበበ እግዚአብሔር ስትወርድ ከመጣች በኋላ ከቅድስት ሀና እና ከቅዱስ እያቄም መወለዷን ገልጿል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
“ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ።” 1ኛ የጴጥሮስ 2: 2
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ለተወደዳችሁ አባቶች፡ እናቶች ወንድሞች እህቶች፡ በሙሉ :
የእግዚአብሔር ሰላም ከሁላችን ጋር ይሁን!
የማኅበረ ቅዱሳን የሰሜን አሜሪካ ማዕከል የትምህርትና ሥልጠና ክፍል በየአስራ አምስት ቀኑ ሲያካሂደው የነበረውን የስልክ ጉባዔ በማጠናከርና ይዘቱን በማሻሻልና ምዕመናን በሚያሳትፍ መንገድ እያካሄደ ይገኛል።
ከዚህም መካከል ተከታታይ የሆኑ ትምህርቶች፡ ከምዕመናን በሚቀርቡ የተለያዩ ጥያቄዎች ላይ የሊቃውንት መልሶችና ውይይቶች ፡ሥነ-ጽሑፎችና ሥነ ግጥሞች ይቀርባሉ።
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የዲሲና አካባቢው ሀገረ ስብከት ከአንድ ዓመት በላይ በትጋት ሲሠራበት የነበረውን የመንበረ ጵጵስና ግዢ በእግዚአብሔር ቸርነት፣ በድንግል ማርያም አማላጅነት በአባቶችና በምእመናን ትጋትና ርብርብ ተግባራዊ ሊያደርግ መቻሉን የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም አበሰሩ። በትንሣዔ ማግስት፣ በቅ/ሚካኤል ወርሃዊ በዓል መታሰቢያ ዕለት እና በማዕዶት ቀን ይህ ታላቅ ዜና መሰማቱ በአገልግሎቱ የተሳተፉትን በሙሉ ከልብ አስደስቷል።
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
|