|

የጽዮንን አሥራት ሀገር፣ የቃል ኪዳኑን ታቦት ምድር፤
በቅዱሳን ጸሎት እሳት፣ በነበልባል የምታጥር፤
ለኢትዮጵያ ተስፋ ፈጻሚ፣ የጉንጯን ዕንባ የምታብስ፤
የተዘረጋ የተማጽኖ እጇን፣ በምሕረትህ የምትዳስስ፣
ቅዱስ ሥጋህን ቆርሰህ፣ በክቡር ደምህ የዋጀኸን፤
ሰማያዊ ምስጢርህን ገልጠህ፣ በተዋሕዶ ያከበርከን
ማዕበል ወጀቡን አሻግረህ፣ ከእሥራ ምዕቱ ያደረስከን
የድንግል ማርያም ልጅ፣ ቸሩ መድኃኔ ዓለም ተመስገን ….
ተመስገን …..
|
|
ዜና
www.eotcdc.org
የዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢዋ ሀገረ ስብከት የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት፣የመንበረ ፓትርያርኩን እና የሀገረ ስብከቱን የሥራ እንቅስቃሴ፣አስፈላጊ የሆኑ ቤተ ክርስቲያናዊ መረጃዎችን እና ዜናዎችን የሚያቀርብበት አዲስ ዌብ ሳይት ከፍቷል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የንባብ፣ የዜማ፣ የቅዳሴ፣ የቅኔ፣ የመጻሕፍት፣ የአቋቋም ወዘተ የአብነት ትምህርት ቤቶች የቤተ ክርስቲያኒቱ እምነትና ሥርዓት ሳይፋለስ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍና የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ አገልግሎት ሳይቋረጥ እንዲቀጥል ጉልህ ድርሻ ተወጥተዋል፣ እየተወጡም ነው፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
በእርጅና ምክንያት ለከፍተኛ ጉዳት የተዳረገው ጥንታዊው የአጋሮ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያንን ለማዳን በሚደረገው ጥረት ምእመናን ድጋፍ እንደያደረጉ የሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ እድሳት ኮሚቴ ሰብሳቢ ጥሪ አቀረቡ፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
ኅብረ ነገር
|
|
አባታችን አባ መቃርስ በሚኖርበት ገዳም ውስጥ ታዎሜጦስ የሚባል ገዳማዊ ነበር፡፡ ይህ ሰው ከገዳሙ እየወጣ ካንዲት ሴት ጋር ይውል ነበርና የገዳሙ አባቶች መጥተው ለአበምኔቱ ለአባ መቃርስ ነገሩት፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
ነገረ ቅዱሳን
ቤተ ክርስቲያናችን ለምን ስለ እመቤታችን ዘወትር እንደምታስተምር አንዳንድ ሰዎች ግር ሲላቸው ይታያል፡፡ እንዲያውም ‹‹አላዋቂ ሳሚ...›› እንዲሉ ስለ እመቤታችን ማስተማå ስለ ጌታችን እንዳታስተምር አድርጓታል ብለው የሚናገሩም አሉ፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን ግን ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የምታስተምረው ለርሷ ካላት ልዩ ፍቅር ብቻ ወይም ስለጌታችን የምታስተምረው ለርሷ ካላት ልዩ ፍቅር ብቻ ወይም ስለጌታችን የምታስተምረው አልቆባት አይደለም፡፡ ምክንያቱም ከኢትዮጵያ ሊቃውንት በላይ ለነገረ መለኰት ምሁርና ጥንቁቅ ከማግኘት የሰማይን ስፋት ልክ ማግኘቱ ሳይቀል አይቀርም፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
ዜና
ከአርብ ግንቦት 15 እስከ 17 ቀን 2000 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ቀናት በሲያትል ከተማ ሲካሄድ የነበረው 10ኛው የማኅበሩ ጉባዔ በተሳካ ሁናቴ ተጠናቀቀ፡፡ የ2001 ዓ.ም ዕቅድ በማጽደቅ፣ ሪፖርቶችን በመገምገምና የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ሁናቴዎች በመገምገም ውሳኔዎችን አስተላልፏል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
ክርስቲያናዊ ሕይወት
የእግዚአብሔርን ስም በከንቱ መጥራት ሲባል ምን ማለት ነው? የአምላካችን የእግዚአብሔር ስም የከበረ በመሆኑ እንደተገኘ የሚጠሩት፣ እንደአጋጠመ የሚናገሩት አይደለም፡፡ ይልቁንም በመፍራትና በመንቀጥቀጥ በትሕትና ሆነው ሊጠሩት የሚገባ ክቡር ስም ነው፡፡ ይሁን እንጂ አንዳንድ ሰዎች የእግዚአብሔርን ስም ያለአግባብ በነገራቸው ሁሉ ውስጥ ሲያስገቡት፣ ሥፍራም ጊዜም ሳይመርጡ እንደፈለጉት ሲጠሩት ይስተዋላሉ፡፡ እንደዚህ ዓይነት ሰዎች እምነትና ፊሪሃ እግዚአብሔር አላቸው ለማለት አያስደፍርም፤ ምክንያቱም የሚያምኑና
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
ነገረ ቅዱሳን
እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል አደረሳችሁ፡፡
የዛሬ 2015 ዓመታት ወደ ኋላ ዘወር ብለን ስንመለከት ታሪክን የሚለውጥ አንድ ድንቅ ክስተት መፈፀሙን እናገኛለን፡፡ ይህም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልደት ነው፡፡ ልበ አምላክ የተባለ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው ያላትም እርሷን ነው (መዝ. 88፡1)፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
|